Media

  1. https://youtu.be/MvVHVK3448U

2. @tikvahethmagazine ባንኩ በበጀት ዓመቱ 3.8 ቢልዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከፍተኛ የፖሊሲ ፎረም በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዚሁ ፎረም ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዮሐንስ በተለይም ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ባንኩ በ2013 ዓ.ም 4.2 ቢልዮን ብር ማትረፉን አስታውሰው በዘንድሮው አመትም 3.8 ቢልዮን ብር ከታክስ በፊት ትርፍ ማግኘቱን ነው የጠቆሙት።
በተጨማሪም ባንኩ በያዝነው ዓመት 19 ቢልዮን ብር ለማበደር አቅዶ 22 ቢልዮን ብር ያበደረ ሲሆን ይህም ከዕቅዱ 120% ምሳደጉን ገልፀው በ2015 በጀት ዓመትም 30 ቢልዮን ብር ለማበደር መታቀዱን አያይዘው ተናግረዋል።
ባንኩ በቱሪዝም፣ በግብርና እና ሌሎችም ዘርፎች በትኩረት እየሰራ መሆኑን ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ ለ33,000 ወጣቶችም በአነስተኛና መካከለኛ ስልጠና መሰጠቱን አንስተዋል።
በመጨረሻም 78 ቅርንፎች ያሉት ባንኩ በቀጣይ 30 ቅርንጫፎችን በመክፈት ወደ 108 በማሳደግ በ22 ዲስትሪክት ተቀዛቅዘው ያሉትን በማጠናከር በትከረት ለመስራት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል።
@tikvahethmagazine

3. #ETHIOPIA
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተለያዩ ጥናት አድራጊዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ፖለቲከኞች በተገኙበት ለ2 ቀናት የቆየ ከፍተኛ የፖሊሲ ፎረም አካሂዷል። 
በፎረሙም በ4 ዋና ጉዳዮች ላይ የትዘጋጁ ጥናቶች ለውይይት ቀርበዋል።
ትልቅ ተፅዕኖ የፈጠረው የሩስያ ዩክሬን ጦርነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ጂዲፒውን በ1% ሊቀንስ እንደሚችልና 71 ሚልዮን የሚጠጋው ህዝብ ደግሞ በዋጋ ግሽበት የተነሳ ከድህነት ወለል በታች ሊገባ እንደሚችል ተገምቷል።
ሀገራችን ኢትዮጵያም 33% የዋጋ ግሽበት ያስተናገደች ሲሆን ከዚህም ውስጥ 13% ሚሆነው በጦርነቱ ምክንያት የመጣ መሆኑ በተደረጉ ጥናቶቾ ተመላክቷል። 
በሀገሪቷም ተጨማሪ 3 ሚልዮን የሚጠጉ ሰዎች ከድህነት ወለል በታች ሊገቡ እንደሚችሉና ጂዲፒያችንም ወደ 7% ሊቀንስ ይችላል ነው የተባለው።
ከ40% በላይ ከሁለቱ ሀገራት ምርቶች የምታስገባው ኢትዮጵያ ነዳጅ፣ ማዳበሪያና ምግብ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ፈጥሮባታል፤ የኮሮና ወረርሽኝ፣ በሀገሪቱ የተከፈተው ጦርነት ፣ የተለያዩ ብድሮች፣ በተፈጥሮ አደጋዎችና ሌሎች ምክንያቶች ግሽበቱን በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር እንደቻለ ተገልጿል።
ለዚህ ሁሉ ችግር ምርታማነትን ማሳደግ፣ የነዳጅ አጠቃቀማችንን ማስተካከል ቢቻል መቆጠብ፣ ማዳበሪያን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ የአረንጓዴ ኋይልን ማጠናከር፣ ግጭትን ማስቆምና ሌሎችም እንደ መፍትሔ ተጠቁመዋል።
የተለያዩ የምርምር ስራዎችን በመስራት ለውይይት የሚያቀርበው ማኅበሩ ባለፈው ዓመት 10 ጥናቶችን ያቀረበ ሲሆን ሌሎች የምርምር ስራዎችንም እንደሚያቀርብ አስታውቆ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ያለ ገለልተኛ ተቋም መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia

4. https://youtu.be/MvVHVK3448U

5. https://www.ethiopianreporter.com/110211/

6.https://www.facebook.com/1490190331223441/posts/pfbid02u1pyww4noqVzyxZWtqkNdwfVhi7T4WGPix87FmBh2mVQVkvXn3HRMupjBNCMH54tl/

7. https://www.ena.et/?p=183251

8. https://www.youtube.com/watch?v=mYpxXg4napU

9. @tikvahethmagazine, @tikvahethiopia

10. https://www.youtube.com/watch?v=4XRROXIiP5Q

11.

Expertise view on the effect on economic sanctions and policy options

Expertise view on financial liberalization in Ethiopia

” ኢትዮጵያ የ ‘ ብሪክስ ‘ ቡድንን የተቀላቀለችው በዋናነት በወቅታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ማዕቀቦች ጫና ነው ” – የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር የባለሙያዎች ዳሰሳ

ከ5 ሺህ 500 በላይ የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን ያቀፈው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ‘ የኢትዮጵያ ብሪክስ ቡድንን መቀላቀል ጥቅም እና ስጋት ’ን የፈተሸ የባለሙያዎች ዳሰሳ አድርጎ በዋና መስሪያ ቤቱ ይፋ አድርጓል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በአካል ተገኝቶ በተከታተለው በዚህ ዳሰሳ የማህበሩ የምርምርና ፖሊሲ ትንተና ዳይሬክተር ደግዬ ጎሹ (ዶ/ር)፤ ” በዳሰሳው 233 የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ” ብለዋል።

የግኝቱ ዋነኛ ነጥቦች ፦

– ከተሳታፊዎች መካከል :

* 49% የሚሆኑ ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የብሪክስ ቡድንን የተቀላቀለችው በፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማዕቀቦች ተገፍታ ነው ብለዋል።

* 47% የሚሆኑት አዳጊ ኢኮኖሚ ስላላት ነው ብለዋል።

* 45.5% የጂኦፖለቲካዊ ምክንያቶችን አንስተዋል።

* 41% እና 39% እንደቅደም ተከተላቸው ከምዕራባውያን ጋር የግንኙነት መሻከር እና የውጭ ምንዛሪ እጥረትን በገፊ ምክንያትነት ጠቅሰዋል።

” ይሄ ትንሽ ተቃርኖ አለው። መንግስት የሚለው በራሳችን በጎ ተግባሯ (merits) ነው ይላል፤ ያመለከተችው በተፅዕኖዎቹ ነው፤ ለምን እንደተቀበሏት አይታወቅም። በእርግጥ ብሪክስ የተቀበላቸው ሀገራት በምን መስፈርት እንደገቡ ማንም አያውቀም ” ሲሉ ዶ/ር ደግዬ ግኝቱን አስረድተዋል።

– ከተሳታፊ ባለሙያዎች ውስጥ ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል ያሉት 51% ሲሆኑ 25% የሚሆኑት በተቃራኒው እንደሚሆን ገምተዋል።

– #ዶላርን ከግብይት ስርዓት ውጪ ለማድረግ ስለተያዘው የብሪክስ ዕቅድ በተመለከተ ይሳካል የሚሉት ብዙኀኑ ቢሆኑም ይህ እንዲሳካ እስከ 15 ዓመታት ይፈጃል ያሉት 67% ናቸው።

ዳሰሳው ሌላኛው የተመለከተው ጉዳይ ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ ከምዕራባውያን ወገኖች ስለምታጣቸው ጥቅሞች እና ስለሚኖሩት ጫናዎች ነው።

በዚህም፦

* ብድር እና ድጋፎችን ለማግኘት ትቸገራለች ወይም ትከለከላለች የሚሉ ባለሙያዎች 56% ናቸው።

* 43% የሚሆኑት በሂደት ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች ገንዘብ ለማሰራጨት ትቸገራለች ብለዋል።

* 40% የሚሆኑት የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም ግፊት ይደረግባታል ብለዋል።

– ጫናዎችን በተመለከተ 66% የሚሆኑት ከምዕራባውያን ዘርፈ ብዙ ጫናዎችን ሲገምቱ፣ በአባላቱ መካከል የእርስ በእርስ የፖለቲካ ፍላጎት ግጭቶች እንዲሁም የብሪክስ ልማት ባንክ የሆነው ” ኒው ዲቨሎፕመንት ባንክ ” አቅም ውስንነት በተከታይነት ስጋቶች ሆነው ተቀምጠዋል።

የባለሙያዎች ዳሰሳው ያስቀመጣቸው ምክረ ሃሳቦች ፦

☑️ የኢኮኖሚ ባለሙያዎቹ ኢትዮጵያ በምዕራባውያን ቁጥጥር ስር ከሚገኙት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም ከብሪክስ ጋር መስራት ግዴታዋ እንደሆነ ገልፀው፤ ለረጅም ዓመታት ከምዕራባውያን ጋር ከነበራት ትስስር አሁን እንደተፃራሪ ወደሚታየው ብሪክስ ቡድን ስትገባ የሁለቱን አሰላለፍ ጥቅምና ጉዳት በትኩረት ለይቶ መንቀሳቀስ ትኩረት እንደሚፈልግ ተገልጿል።

☑️ እስከዛሬ ከምዕራባውያን የሚገኙ ጥቅሞችን ማካካስ ካልቻለ ተግዳሮቱ ይበዛል። የዶላርን የበላይነት መቀነስና ለንግድ የራሳቸውን ኖቶች መጠቀም የሚለውም ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ እጥረት የባሰ ራስምታት ስለሚሆን ከአባል ሀገራቱ የሚኖረውን አንድነትና ልዩነት በአግባቡ መፈተሽ ይገባል።

☑️ ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስተማማኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር የሚያሰራ የፋይናንስ ስርዓት ለመፍጠር መልሶ ማደራጀት ይፈልጋል ብለዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia

Menaheria FM: Migration and Labor Market

Menaheria FM: The Implication of Government Policy Toward EV Local Economy

Ethiopian Economics Association

Ask any information related to membership inquiries.

Hello, Welcome to the site. Please click below button for any membership inquiries.